ዜና

የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የ2014 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር እቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡ - ዓርብ ፣15 ኤፕሪል 2022

ሚያዚያ 06 ቀን 2014 ዓ.ም የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የ2014 በጀት ዓመት የዘጠኝ (9) ወር እቅድ አፈፃፀም የኮሚሽኑ ፕሬዚደንት ፣ ዳኞች ፣ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት ቦሌ በሚገኘዉ ሳቦን ሆቴል ተገምግሟል፡፡
የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ፕግራሙን ያስጀመሩት የኮሚሽኑ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሙሉጌታ አያሌዉ  መንግስትና ህዝብ የጣለብንን ሀላፊነት ነፃና ፣ ገለልተኛ በሆነ መልኩ በመስራ ለሌሎች ተቋማት አርዐያ በመሆን የንግዱን ማህበረሰብ የሚያምንብን በህግ እና በመመሪያ ላይ በመመርኮዝ ፈጣን አገልግሎት መስጠት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
በመቀጠል ኮሚሽኑ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወር ጊዜ ዉስጥ በአጠቃላይ የቀረቡ የቅሬታ መዛግብቶች ከገቢዎች 372 ከጉምሩክ 494 በአጠቃላይ 866 ሲሆኑ ከነዚህ ዉስጥ በዘጠኝ ወራት ዉስጥ አዲስ የተከፈቱ ከገቢዎች 193 ከጉምሩክ 336 በአጠቃላይ 567 ሲሆኑ ከነዚህ የቅሬታ መዛግብት ዉስጥ 529ኙ ሲወሰኑ የተቀሩት ለመልስ 40 ፣ ለብይን 3 ፣ ለቃል ክርክር 292 እና ለዉሳኔ 2 በድምሩ 337 መዛግብት ወደ አራተኛ ሩብ ዓመት ተሸጋግረዋል ብለዋል፡፡
አያይዘዉም ጊዜዉ \ቴክኖሎጂ እንደመሆኑ መጠን ኮሚሽኑ አዲስ ባስገነባዉ ዳታ ቤዝ ባለድርሻ አካላቶቿችን ሳይጉላሉ ካሉበት ቦታ በመሆን ጉዳያቸዉን ወይም ቅሬታቸዉን በWWW.ftac.gov.et በመመዝገብ መከታተል እንደሚችሉ ገልፀዋል፡፡
የኮሚሽኑን የ2014 የዘጠኝ (9) ወር የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡት የኮሚሽኑ ፕላንና ለዉጥ ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ እዮብ አለማየሁ የዉሳኔ የመስጠት አቅም ለማሳደግ ለዉሳኔ ከተቀጠሩት 531 መዛግብት ዉስጥ ለ529 መዛግብት ዉሳኔ በመስጠት የዉሳኔ የመስጠት አቅማችን 99.6 የደረሰ መሆኑን እና ከባለፈዉ ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነፃፀር በ5.6 መሻሻል ያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በመጨረሻም የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበዉ የ2014 የዘጠኝ (9) ወር የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን አቅርበዉ  ሰፊ ዉይይት የተደረገበት ሲሆን በቀጣይም ምን መሆን እንዳለበት በኮሚሽኑ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሙሉጌታ አያሌዉ ቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛ አድራሻችንን ይጠቀሙ
ቴሌግራም
http://t.me/FTAC2014
http://www.facebook.com/taxapco

 

 
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት እና አመራሮች የዲጂታል ሀብት ምዝገባ አካሄዱ፡፡ - ማክሰኞ ፣29 ማርች 2022

የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት እና አመራሮች የዲጂታል ሀብት ምዝገባ አካሄዱ፡፡

********************

የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን መጋቢት 15 ቀን 2014 ዓ.ም የኮሚሽኑ ፕሬዝዳንት ፣ ዳኞች ፣ አመራሮችና ሰራተኞች በኮሚሽኑ ፅ/ቤት የዲጂታል ሀብት ምዝገባ አካሄዱ፡፡

 

በዲጂታል የሀብት ምዝገባ ስነ-ስርዓቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሙሉጌታ አያሌዉ የሀብት ምዝገባ ዲጂታል ስርዓት ከወረቀት ነፃ ሆኖ ሀብትን በበየነ መረብ ለማስመዝገብ የሚያስችል የመረጃ ጥራት እና ተደራሽነት የሚጨምር ጊዜ ፣ ወጪ ቆጣቢ ፣ ግልፅነት ፣ ተጠያቂነት ለማስፈን እና የጥቅም ግጭትን ለመከላከል የሚረዳ ነዉ በማለት የዲጂታል ሀብት ምዝገባዉን በቀዳሚነት በመመዝገብ አስጀምረዋል፡፡

 

አያይዘዉም ሁሉም የኮሚሽኑ ዳኞች አመራሮች እና ሰራተኞች ዲጂታል የሀብት ምዝገባ የአሰራር ስርዓት የሚጠይቀዉን በሙሉ በቅንነትና በታማኝነት መመዝገብ እና ሌሎችም እንዲያስመዘግቡ ማበረታታት እና  ሀገራዊ ግዴታቸዉን እንዲወጡ አበክረዉ ተናግረዋል፡፡

 

የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይክቶሬት ጀማሪ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሪት ትዕግስት ጥላዬ ስለ ዲጂታል የሀብት ምዝገባ የአሰራር ስርዓት ለኮሚሽኑ ዳኞች ፣ አመራሮች እና  ሰራተኞች ኦሬቴሽን ሰተዋል፡፡

 

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛ አድራሻችንን ይጠቀሙ

ፌስ ቡክ

https://www.facebook.com/taxapco

ቴሌግራም

https://t.me/FTAC2014

 
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በ2014 ግማሽ ዓመት ከ 1 ቢሊዬን በላይ የብር መጠን ያላቸዉ መዝገቦች ላይ ዉሳኔ ሰጠ - ማክሰኞ ፣29 ማርች 2022

የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በ2014 ግማሽ ዓመት ከ 1 ቢሊዬን በላይ የብር መጠን ያላቸዉ መዝገቦች ላይ ዉሳኔ ሰጠ

********************

የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በ2014 ግማሽ ዓመት ለኮሚሽኑ ከቀረቡት የይግባኝ መዝገቦች መካከል 1,422,503,508.00 የብር መጠን የያዙ 307 የይግባኝ መዝገቦች መርምሮ ወሳኔ ሰጠ ፡፡

 

ኮሚሽኑ በ2013 በጀት ዓመት ዉሳኔ ሳያገኙ ወደ 2014 በጀት ዓመት የዞሩ 299 መዝገቦችን በማካተት በ2014 በጀት ዓመት የጉምሩክ ኮሚሽን 187 የገቢዎች ሚኒስቴር 181 በድምሩ 368 አዲስ የተከፈቱ መዝገቦችን በመያዝ በድምሩ 667 ዉሳኔ የሚሹ የይግባኝ መዝገቦች ለኮሚሽኑ ቀርቦ የታየ ሲሆን ከ667 መዝገቦች መካከል ለ312 የይግባኝ መዝገቦች ዉሳኔ ለምስጠት ተቀጥረዉ ለ307 የይግባኝ መዝገቦች ዉሳኔ መስጠት ተችሏል፡፡

 

በኮሚሽኑ ዉሳኔ ከተሰጣቸዉ የይግባኝ መዝገቦች መካከል 52 የተሻረ ፣ 15 የተሻሻለ ፣ 187 የፀና ፣ 41 የተዘጋ እና 12 የተመለሱ መዝገቦች ሲሆን በ2014 ግማሽ ዓመት ከ 307 ዉሳኜ ካገኙት መዝገቦች ዉጭ ያሉት 360 መዝገቦች መካከል 47 ለመልስ ፣ 3 ለብይን ፣ 305 ለቃል ክርክር እና 5 ለዉሳኔ የተቀጠረ ሲሆን የኮሚሽኑ የዉሳኔ መስጠት አቅም 98.39% የደረሰ ሲሆን የአፈፃፀም ዉጤት ከ2013 የግማሽ አመት አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር በ2.59% መብለጥ ችሏል፡፡

 

በተጨማሪም በ2013 የዞሩ እና በ2014 ግማሽ ዓመት ከቀረቡ የይግባኝ መዝገቦች ከገቢዎች ሚኒስቴር 270 የይግባኝ መዝገቦች ሲሆኑ የያዙት የገንዘብ መጠን 1,605,082,317.83 ሲሆን ከጉምሩክ ኮሚሽን የቀረቡ የይግባኝ መዝገቦች ብዛት 397 ሲሆን የያዘዉ የገንዘብ መጠን 838,095,788.97 ነዉ፡፡

 

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛ አድራሻችንን ይጠቀሙ

ፌስ ቡክ

https://www.facebook.com/taxapco

ቴሌግራም

https://t.me/FTAC2014

 
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተገለጸ - ረቡዕ ፣2 ሴፕቴምበር 2020

የፌዴራል ታክስ ይግባኝ የኮምሽን ፕሬዝዳንት አቶ ሙሉጌታ አያሌው ኮሚሽኑ በአዲስ መልክ በአዋጅ ቁጥር 983 /2008 ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል፡፡

የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን፣ ውጤታማ፣ ፈጣን ተደራሽ ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለው ተቋም መገንባትን ራዕይ በማንገብ የታክስከ ፋዩን ማህበረሰብ ቅሬታ በተደራጀና በተፋጠነ መልኩ መፍታት አላማው አድርጎ መቋቋሙን አስታውሰው ለተግባራዊነቱ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡

እንደ አቶ ሙሉጌታ ገለጻ፣ ኮሚሸኑ በታክስ ሕጎች አተረጓጎም ረገድ በታክስ አስተዳደሩ ውስጥ በሚፈጠረው ልዩነት ምክንያት ታክስ ከፋዩ ሲያጋጥመው የነበረውን እንግልት ለማስቀረት የሚያስችል ወጥነት ያለው የአተረጓጎም ስርዓት እንዲኖር ከማድረጉም በተጨማሪ ታክስ ከፋዮች የሚኖራቸውን ቅሬታ ማቅረብ የሚችሉበት ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ በአዲስ መልክ እንዲደራጅ ተደርጓል፡፡

በአዲስ መልክ ስራውን ከጀመረ 8 ወራትን ያስቀጠረው ተቋሙ ቀደም ሲል በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ጽ/ቤት ተብሎ ይጠራ እንደ ነበር ያስታወሱት የኮሚሽኑ ፕሬዝዳንት፣ መንግስት ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት እና የህብረተሰቡን ችግሮች በተቀላጠፈ መንገድ ለመፍታት እንዲያስችል ራሱን ችሎ በኮሚሽን ደረጃ መቋቋሙን ገልጸዋል፡፡

ስራው ቀደም ሲል ከጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ ከንግዱ ማህበረሰብ፣ ከገቢዎችና ሌሎች ጋር በጋራ በመሆን በኮሚቴ መልክ የሚሰራ ስራ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በርካታ ችግሮች የነበሩ በመሆኑ ይህንን ለመቅረፍ በሞያቸው ገለልተኛ የሆኑ ዳኞች እንዲሾሙ ተደርጓል ብለዋል አቶ ሙሉጌታ በንግግራቸው፡፡
ኮሚሽኑ በአዲስ መልክ ከተደራጀ በኋላ የተቋሙን መዋቅር የመስራትና የማፀደቅ፣ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶችን የመቅረፅ፣ የተቋሙን መሪ እቅድ፣ እንዲሁም ለተቋሙ ስራ የሚረዱ መመያዎችንና ደንብቦችን በማውጣት ረገድ የታክስ ከፍዩን ማህበረሰብ እንግልት በሚቀንስ መልኩ በመስራት ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

ተቋሙ 930 መዝገቦችን የመረመረ ሲሆን 423 መዝገቦች ተሰርተው የተጠናቀቁ ፣ 359 መዝገቦች ለክርክር በሂደት ላይ ያሉ እና 148 መዝገቦች ደግሞ በቀጣይ አጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አቶ ሙሉጌታ ተናግረዋል፡፡

ተቋሙ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማዳበር፣ የህግ ክፍተቶችን ለመለየት እና ችግሮች ላይ ለመምከር በቀጣይ የተለያዩ መድረኮችን እንደሚያዘጁም የኮሚሽኑ ፕሬዝዳንት ጠቁመዋል፡፡

በመጨረሻም፣ መንግስት የግብር ከፋዩን ማህበረሰብ ቅሬታ ለመፍታት ገለልተኛ የሆነውን የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የተቋቋመ በመሆኑ፣ ማንኛውም በሚከፍለው ታክስ ቅር የተሰኘ አካል አቤቱታውን ለታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በማቅረብ የታክስ አስተዳደሩ ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተገማች እንዲሆን የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት አቶ ሙሉጌታ ጥሪ አቅርበዋል፡፡